ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ነው ። ወ/ ሮ ሚልድሬድ ማሼጎ እና የአብራካቸው ክፋይ የሆነችው ፓትሪሲያ ስማቸው የአለማችን የድንቆች መዝገብ ውስጥ የሰፈረው።
በደቡብ አፍሪካ ካስቲል ነዋሪ የሆኑት የ38 አመቷ እናት ወ/ሮ ማሼንጎና የ19 አመቷ ወጣት ልጃቸው ፓትሪሲያ በአንድ ወር ውስጥ፣ በአንድ ሣምንት ውስጥ እንዲሁም ከተመሳሳይ ሰው በመውለድ ወ/ሮ ማሼንጎ ልጅና የልጅ ልጅ አገኙ ፣ ወጣት ፓትሪሲያ ልጅና ወንድም አገኘች እንዲሁም አቶ ቪንሴንት ማሉማን እናትና ልጅ በአንድ ሣምንት ውስጥ አስረግዘው ከዘጠኝ ወራት በኋላ የሁለት ወንዶች ልጆች አባት ሆኑ።
እናት እርጉዝ በነበሩበት ወቅት ልጃቸው ፓትሪሲያም እንደ እሳቸው ነፍሰጡር መሆኗን የተረዱ ቢሆንም ያረገዘችው ግን እሳቸውን ፅንስ ካሲያዛቸው አቶ ቪንሴንት ማሉማን መሆኑን በፍፁም አልገመቱም ነበር። ለዚህም ይመስላል የወ/ሮ ማሼንጎ ንዴትና ድንጋጤ ከፊታቸው ይነበብ የነበረው ።
ሌላው አስገራሚ የነበረው አቶ ቪንሴንት አስቀድሞ ያስረገዘው የወይዘሮዋን ልጅ መሆኑ ነዉ። አስቀድሞም ምጥ የመጣው የልጅ ፓትሪሲያ ነበር። ልጅ ፓትሪሲያ በአካባቢያቸው ወደሚገኘው የማዋለጃ ክሊኒክ በመሄድ ወንድ ልጅ ከነቃጭሉ በተገላገለች በአራተኛው ቀን ወላጅ እናቷም በዚያው ክሊኒክ ለእርሷና ለልጇ ታናሽ ወንድም አበርክተውላቸዋል።
አልሞ…
View original post 22 more words